Posts

Showing posts from December, 2022

የሰው ልጆችን ነፃነት (humans freedom )ምንድን ነው?

Image
  ከወሰንሰገድ መርሻ (ጮራ ዘአራዳ )     በአንድ አገር ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ነፃነት ያስፈልጋቸዋል። የመናገር ወይንም    ሀሳብን የመግለፅ ነፃነት ፤ከአንዱ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በሰላም የመንቀሳቀስ ወይንም    በሰላም ወጥቶ በሰለም    የመግባት ነፃነት፤የዲሞክራሲ ነፃነት፤የፖለቲካ ነፃነት ፣የማህበረሰብ    ነፃነት ፤የኢኮኖሚ    ነፃነት፤የፍቅር ነፃነት፤የጓደኝነት ነፃነት ወዘተ.  አሉ።   በዓለማችን ያሉ ታላላቅ የፍልስፍና ሰዎች ነፃነትን (freedom )   በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፋፍሉታል።   በአንደኝነት       የነፃነት አሳብ ብለው የሚያስቀምጡት ሰዎች በእርስ በርስ ግንኙነታቸው    ወቅት በአሳባቸው    ውስጥ    የፀነሱትን የነፃነት    (freedom ) ከማህበረሰቡና ከመንግሥት አስተሳሰብ ጋር ባልተቃረነ መልኩ አብረው    የሚኖሩትን ሕይወት ይመለከታል። በማለት ይገልጻሉ።      ሁለተኛው    ደግሞ ከመጀመሪያው    ፍፁም የተለየ የሆነው    የነፃነት እሳቤ ደግሞ    የሰው    ልጅ    በዕለት ተዕለት ድርጊቱ የሚፈፅመውን ድርጊት የሚወስንበት የራሱ የሆነ ውስጣዊ የሆነ ነፃነት አለው    በማለት ይገልጻሉ።በሌላ አነጋገር ይህን «ስነልቦናዊ ነፃነት»(psychological freedom )በማለት ይጠሩታል።    ሦስተኛውና የመጨረሻው የሰው ልጅ በውስጡ    ከሚነሱት ግጭቶች (conflict)    ነፃ የሚሆኑበትና ተፈጥሮውን ወደ   ፍፁምነት በማድረስ ሊሆን የሚገባውን የነፃነት ሀሳብ የሚንሸራሸርበትና የሚጨብጥበት አንዱ የነፃነት አካል ነው። በማለት ይጠቁማሉ።    በእርግጥ      አንዳንድ ፈላስፎችና የስነመለኮት ምሁራኖች የሰው

ጃፓን ውስጥ ከትዳር ውጭ መማገጥ የተለመደ ነው

Image
    ከወሰንሰገድ መርሻ (ጮራ ዘአራዳ) ጃፓናውያን ሲያወሩ በሹክሹክታ መሆኑን ከዚህ ቀደም ሰምተው ወይም  ይሆናል። አብዛኛዎቹ ጃፓናውያን እራሳቸውን የመደብቅ ፍላጎት አላቸው ። በተለምዶ በዎኪ-ቶኪ-በያዙ ሰራተኞች የሚጠበቁ ባለሀብቶች ወይም ባለስልጣኖች ሊኖሩ ይችላሉ።እነዚህ ጥብቅ የሆነ ማንነትን የመደበቅ ሁኔታ የተለመዱ ነገሮች ናቸው ።ለመዝናናትም እንደዛው ነው።አብዛኛው  የጃፓን የምሽት ክበቦች ወይም  መጠጥ ቤቶች ድብቅ የሆኑ ናቸው።ይህ ደግሞ ስም-አልባ  የሆኑና ያልተወሳሰቡ ነገሮች  ከጭንቀት ነፃ ሆነው  እንዲዝናኑ ያደርጋቸዋል።በተለይም  በባላቸው ወይም በሚስቶቻቸው ላይ ለሚማግጡ  ባለትዳሮች ምቹ በመሆናቸው  የምሽት ክበቦቹ ሰዎችን ይስባል። ነገር ግን ደንበኞቻቸው ከጊዜ በኋላ አንዳንድ ጊዜ እዛ ምሽት ቤት የሚያዘወትሩ ጃፓናውያን ከበርካታ ድግግሞሾች በኋላ ማወቅ የሚቻለው  ሲተዋወቁ ያገባ ወይም ያገባች መሆኑን ማወቅ የተለመደ ነው።  በአጠቃላይ ከደንበኞች ውስጥ ግማሽ ያህሉ ባለትዳሮች ናቸው። ይህም  ማለት በመታጠቢያዎቹ ገናዳ ውስጥ ያለው ሽታ የሌለውን  ሳሙና ይይዛል  እንደማለት ይቆጠራል።  እ.ኤ.አ. በ 2020 አሀዛዊ መረጃ መሠረት 20 በመቶው የጃፓን ህዝብ የትዳር ጓደኞቻቸውን ማጭበርበርበራቸውን  ይናገራሉ።  ከጥቂት ዓመታት በፊት የፔው የምርምር ማዕከል ጃፓንን ማጭበርበር 'በሥነ ምግባር ደረጃ ተቀባይነት ያለው ' ነው  ተብሎ በሚታሰብባት የዓለም  ሀገራት ውስጥ ጃፓን ሰባተኛዋ አገር እንደሆነች በመግለጽ አንድ ጥናት አስቀምጧል። በእርግጥ  በጣም ምክንያታዊ ያልሆነ ይመስላል።ይሁንና  ብዙ ጊዜ እንደዚህ አይነቱ ሁኔታ ይከሰታል። ያገቡ ሰዎች  ልጆች ይወልዳሉ ። ብዙ ጊዜ ሰዎች ትዳር መስርተው ልጅ ሲወልዱ ከ

የውጭ ዜጎች ወደ ጃፓን የመሄድ ፍላጎት እየቀነሰ ነው

Image
  ከወሰንሰገድ መርሻ (ጮራ ዘአራዳ)       የጃፓን ጽሑፍ የለህም  ወይ ያላችሁኝ አላችሁ።ካለፈው ስህተቱ ለሚማርበትና ለመማር ዝግጁ ለሆነ ሰው ፖስት የተደረገው ብቻ በቂ ይመስለኛል።አንዳንዴ ሳስበው ጃፓን ከሚኖረው ይልቅ ጃፓን የማይኖረው ሰው  ጃፓንን በተመለከተ ያደረኩትን ፖስት  የሰጡኝ አስተያየና  ጃፓን ሆኖ አንዱንም ሳያነብ ጉራ የሚነፋው ሁሉ አባቶች እንደሚሉት '' አስቀድሞ  ነበር፤ መጥኖ መደቆስ አሁን ምንያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ ።''የሚለውን አባባል እንዳስታውስ አድርጎኛል።  ለዛሬው በጃፓን   የውጭ    አገር ነዋሪዎች ቁጥር እየጨመረ  ቢሆንም ከሌሎች ሀገሮች ጋር ሲነፃፀር ፤በጃፓን የሚገኙ የጥገኝነት ጠያቂዎች ምላሽ ከኢሚግሬሽኑ አሉታዊ መሆን እንዲሁም የኢሚግሬሽኑ አባላቶች አስገድደው የውጭ ሀገር ስደተኞችን ወደ ሀገራቸው መላክ ወደ ጃፓን የውጭ ሀገር ዜጎች የመግባት ፍላጎት መቀነሱን  NHK የተሰኘው ተዋቂው የጃፓን ሚዲያ ገልጿል።   ።     የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር  እንደገለፀው እ. ኤ .አ  በ2018 2 ነጥብ 49 ሚሊየን  የውጭ ሀገር ዜጎች በጃፓን እንደሚኖሩ ገልጾ ነበር ።ነገር ግን አዲስ ጥናት እንዳመለከተው    ከአምስቱ ጃፓናውያን መካከል አንዱ ብቻ  ነው  የውጭ ሀገር የስራ ባልደረባ እንዳለውና  እነዚህ   የውጭ ሀገራት  ሰዎች ጃፓንን የመጎብኘት  ፍላጎት  እንደሌላቸው የገለፀ  ሲሆን በዚህም  የተነሳ ጃፓንን የመጎብኘት  ፍላጎት  እየቀነሰ  መምጣቱ  ተጠቁሟል  ።   የኤንኤችኬ ብሮድካስቲንግ ባህል ጥናትና ምርምር ተቋም በየ 5 ዓመቱ ለውጭ ሀገር ዜጎችና ለውጭ ሀገራት ያለውን አመለካከት ዳሰሳ ያደርጋል።  የቅርብ ጊዜ ውጤቶች የጎ

ኢትዮጵያችን እንደ ጁሌስ ኔየሬሬ አይነት መሪ መቼ ይሆን የምታጋኘው?

Image
  ‎   ከወሰንሰገድ መርሻ (ጮራ ዘአራዳ)     የእኛ  ሃገር  ፖለቲከኞች  በነፈሰበት  በኩል  የሚሄዱ ናቸው።ስልጣንና  ጉልበት ያለው  ወገን  ሲያጋሳ  አብሮ   ማጋሳት።ሲተነፍስ  አብሮ  መተንፈስ ፣ሲያስካኩ  አብሮ ማስካካት፤ የማያስቅ  ነገር  አውርቶ  ከሳቀ  እነሱም  ጣራ  እስከ ሚቀደድ  ድረስ  መሳቅ  የተለመደ  ከሆነ  እነሆ ሰነባባተን ።ለመሆኑ  ኢትዮጵያችን  እንደ ጁሌስ ኔየሬሬ  አይነት መሪ መቼ  ይሆን የምታጋኘው?     በፊት  ጁንታው  ዛሬ ደግሞ ወዳጃችን የምንለው   ወያኔ የራስን እድል በራስ መወሰን የሚለውን ሁኔታ ተቀብሎ  መተግበር የጀመረው ከጆሴፍ ስታሊን ፍልስፍና  ነው  ።      ጆሴፍ  ስታሊን  የሌኒንን ሚስት  ጨምሮ  ብዙዎቹን የአገሪቱን ዜጎች  ገድሏል። አንዳንድ  የሶቭየት  ኅብረት ሙሁራኖች    እንደሚገልጹት ከ100 ሚሊዮን  በላይ  የሚጠጉ የሶቭየት ኅብረት ዜጎችን ገድሏል በማለት ይገልጻሉ።    በአንፃሩ  የጆሴፍ  ስታሊን  ደጋፊዎች  ደግሞ  የሟቾች ቁጥር ከ40 ሚሊዮን  አይበልጥም  ብለው ይከራከራሉ።ሆኖም  በሕግ  ፊት አይደለም  አንድ  ሰው መግደልና ያለአግባብ  ሕግን አዛብቶ  ማሰርና ማንገላታት በእግዚአብሔር ዘንድም  እንደሚያስጠይቅ    እሙን    ነው።     ጆሴፍ ስታሊን ከሚታወቅበት ዋንኛው  ነገሮቹ መካከል  ፤ ዜጎችን ተዋቂ  በሆነው  የስለላ ድርጅቱ ኤንኬቪዲ አማካይነት ፤ ሰውን መግደልና  ማሰር ብቻ አይደለም  ዋናው ተግባሩ ።አገሪቱን እረግጦ  ለመግዛት  ፤ ካለው  ፍላጎት   አንፃር የሕዝቡን የሰበአዊ መብቶችን በመግፈፍና ሕዝቡን ረግጦ  በመያዝ  ለበርካታ አመታት ሶቭየት ኅብረትን ለመግዛት በቅቷል።      ይህን የስታሊን    የአገዛዝ ሥርዓት  ፤ አብዛኛዎቹ የሦስተኛው  ዓለ