Posts

Showing posts from May, 2022

እነ አሳማዎች!

✅ እነ አሳማዎች! ከወሰንሰገድ መርሻ (ጮራዘአራዳ) «የጠገበ አሳማ ከመሆን የራበው ሰው መሆን እጅግ የተሻለ ነው።» የሚለውን አባባል የተናገሩት ተዋቂው ፈላስፋ ስቱዋርት ሚል እና ፕሌቶ ናቸው።እንደ ስቱዋርት እና ፕሌቶ አገላለጽ ይህ አባባል የተጠቀሙት ተዋቂው ፈላስፋ ሶቅራጥስ ብዙ እያወቀ ነገር ግን እንደሌሎቹ እራሱን አዋቂ ነኝ እያለ ሳይኮፈስ እንአላዋቂ ሆኖ የተገኘ ፈላስፋ ስለነበረ ነው።  ለዚህም ነው ስቱዋርት ሚል «የጠገበ አሳማ ከመሆን የራበው ሰው መሆን እጅግ የተሻለ ነው።»ያለው።ይህንንም ሲያብራራ« የጠገበ ሰነፍ ሰው  ከመሆን ደግሞ የተራበ ሶቅራጥስ መሆን በጣም ይሻላል።አሳማውም ሆነ ሰነፉ ሰው የሚኖራቸው የራሳቸው ሐሳብ ብቻ ነው። በአንፃሩ  ግን በሁለቱም ወገን ያለውን ሐሳብ በሚገባ ያውቁታል። »በማለት ይገልጸዋል።በእርግጥም ሆዱን ከቆለለ ማህይም ሀብትም ይልቅ።ምንም የሌለው ብዙ ለማወቅ የሚጥር፤ራሱን እንደ አላዋቂ የሚመለከት ፈላስፋውን ሶቅራጥስ አይነት ደሀ መሆን ይሻላል ነው ያለው ስቱዋርት ሚል ። የፕሌቶም አስተሳሰብ ሰው የቱንም ያህል የምግብ ፍላጎት(ሥጋዊ ጥያቄው)ተሟልቶ ሞራላዊውን ጥያቄ ካልመለሰ  ወደ እንስሳነት መውረዱ አይቀሬ ነው ይላል። እንዲያውም ፕሌቶ በዚሁ ጉዳይ ላይ ሲናገር «ከጠገበ አሳማ የራበው ሶቅራጥስ ይሻላል » በማለትም ገልጿል። ልክ እንደ  ሶቅራጥስ ባንሆንም ብዙዎቻችን በዕውቀት የተራብን  እንኖራለን።ብንማር የማይሰለቸን ፤አሊያም ለማወቅ ያገኘነውን ሳንመርጥ ብዙ ማንበብ የምንፈልግ ሰዎች ብንኖርም ያነበብናትን ትንሿን ወይንም ቁንጥሯን ዕውቀታችንን ይዘን ግንብዙ የምናወራ በርካቶች ነን።ስለ ፖለቲካ ሲወራ ተዋቂ ፖለቲከኛ፤ስለ ማህበራዊ ሕይወት ሲወራ የማህበራዊ ሕይወት ጠበብት ወይም ሀያሲ ፤ስለ ስፖርት

ከድህነት መቼ ነው የምንወጣው? ከወሰንሰገድ መርሻ (ጮራ ዘአራዳ)

✅ ከድህነት መቼ ነው የምንወጣው? ከወሰንሰገድ መርሻ (ጮራ ዘአራዳ)  ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ከሰሀራ በታች ካሉ  ድሀ ከሚባሉት አግሮች አንዷ ነች።  ለድህነታችን መንስሄ የሆኑ ምክንያቶች የተለያዩ ቢሆንም ዋና ዋና ዎቹ ምክንያቶች አብዛኛው ሕዝቧ በግብርና ላይ የተሰመረተ በመሆኑ ኋላ ቀር አስተራረስ መጠቀም፣የመልካም አስተዳደር ችግር (እጦት)፣ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የእርስ በርስ ግጭቶች  መከሰት ፣ ባለሀብቶች በየቦታው ተንቀሳቅሰው እንደፈለጉ አለመስራት፣ባለስልጣኖቻችን ከአገር ጥቅም ይልቅ የግል ጥቅማቸውን በማስቀደም በሙስና መጨማለቅ፣በመሰረት ልማቶች ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ከማፍሰስ ይልቅ ለጦር መሳሪያና ለመሳሰሉ አላስፈላጊ ወጪዎች ላይ ማተኮር ወዘተ. ናቸው።  በአደጉ አገሮችም በእርግጥ ድህነት እንደኛ ድሀ በሆኑ የአፍሪካ አገሮች አይነት ሆኖ ባይጋነንም  ድሀ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች አሉ።ልዩነቱ የአደጉ አገሮች ድሀ የሚባሉት በቀን አንዴ ብቻ ሳይሆን በቀን ሦስቴይመገባሉ።  ስለ ድህነት ያጠኑ ወገኖች እንደሚገልጹት «አንዳንድ ሰዎች ከሌሎች ያነሱ ድሆች ናቸው።ስለዚህ የድህነት መገለጫው ደደብነትና የአእምሮ ደካምነት ነው» ይላሉ።እንደ ጥናት አቅራቢዎች አገላለጽ ከሆነ ድህነት መሠረቱ የአእምሮ ደካምነትና ደደብነት እንደሆነ ይገልጻሉ። «በደደብነታቸው ድሆች የሆኑ ሰዎች (Downtree people)ድሆች ልጆችንም ይወልዳሉ።ብልሆች እየከበሩ፤የአእምሮ ብስለታቸው አነስተኛ የሆኑት ግን እየደኸዩ ይሄዳሉ » በማለት ዳውን ትሪ ትረስት(Downtree trust Report) ያወጣው ዘገባ ያስረዳ ነበር።  ይህ አይነቱ ዘገባ ራሳቸው ሪፖርቱን ያወጡት እንግሊዞች  በነሲብ  ያወጡት ብቻ ሳይሆን ደደቦች መሆናቸውን ጭምር የሚያሳይ ነው።  በእኔ እምነት ድህነት

የዘር ጭ ፍጨ ፋው አስከመቼ ❗️

➡ የዘር ጭ ፍጨ ፋው አስከመቼ ❗️ ከወሰንሰገድ መርሻ ከጮራ ዘአራዳ) (ደራሲ፣ጋዜጠኛና ማህበራዊ ሀያሲ)     የዘር ጭፍጨፋ  በአገራችን ውስጥ እንደ ባህል የተቆጠረ ይመስላል።ምክንያቱም ዜናውን ሰምተን በዝምታ የማለፉ ሁኔታ የተለመደ ሆናል። « በቤን  ሻንጉል ጉሙዝና በትግራይ ክልል ዘርን ተኮር ያደረግ ጭፍጨ ፋ ተካሄደ፣በአማራ ክልል እከሌ በተባለ ቦታ አንድን ብሄር መሰረት ያደረገ ጭፍጨፋ ተከናወነ፣በአፋር ክልል እንደዚህ የሚ ባል ቦታ ላይ ጭፍጨፋ ተደረገ ።» የሚሉ ብላ ብላ ወሬዎች መስማቱ ከአሳዛኝነቱና ከ እምባ ማስረጨ ቱ አልፎ ከንፈር መ ጦ ማለፍ የተለመደ ክስተት ሆናል።  ይህ አንድን ብሔር ተኮር ያደረገው የዘር ጭፍጨፋና ሠላማዊ ሰዎችን በታጣቂዎች በግፍ የሚገደሉበት አሳዛኝ ሁኔታ ለምን ማስቆም ተሳነን? የሰው ልጅን የሚያህል አምላካችን በአምሳያው አድርጎ አሳማምሮ የፈጠረውን ፍጡር እንደ ከሰልና እንጨ ት ቤት ውስጥ እያለ በእሳት መማገዱ ፤ በካራና በጥይት ሕፃን አዋቂ ሳይባል መግደሉ፤ ኢትዮጵያውያኖች ስንባል የአባቶቻችን አምላክ እርቆን ምን ያህል እርኩስ መንፈስ የተጠናወተን መሆናችንን የሚያሳይ ነው። እኔም ሆንኩኝ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተው ይህ  አንድ ብሔርን ተኮር ያደረገው የዘር ጭፍጨፋ ልባችንን የነካ ጉዳይ ሆኖ ብቻ ማለፍ የለበትም ። የኢትዮጵያ መንግሥትም ቢሆን ድርጊቱን በፈጸሙት ላይ በተደጋጋሚ እርምጃ እንደወሰደና ወደ ፊትም በዝምታ እንደማይልፍ በተደጋጋሚ ሲነግረን ቆይቷል ።ነገር ግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ሃገሪቱን የሚመራው መንግሥት ለምን ጭፍጨፋውን ማስቆም ተሳነው።በእርግጥ በዚህ ዙሪያ

ኢትዮጵያ እንደ ሰፊው ሕዝብ መሆን አለባት❗️ ከወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ

ኢትዮጵያ እንደ ሰፊው ሕዝብ መሆን አለባት❗️ ከወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ (ደራሲ፣ጋዜጠኛናማህበራዊ ሀያሲ) አገራችን ላለፉት  በርካታ አመታት የተለያዩ ውጣ ውረዶችንና መሰናክሎችን አልፋ ነው አሁን ያለችበት ደረጃ የደረሰችው።እነዚህ ውጣ ውረዶችን ለማለፍ ደግሞ የበርካታ አገር ወዳድ ሕዝቦች እስርና እንግልት ወይም መከራ  የከፈሉት መስዋትነት ይጠቀሳል።  ሰዎች ስንባል እንደ አሻራችን አስተሳሰባችንም የተለያዩ ናቸው።ያለፈውን የወያኔ አገዛዝ የሚቃወም እንዳለ ሁሉ የሚደግፍም አለ።የአሁኑን የዶክተር አብይ መንግስትን የሚደግፍ እንዳለ ሁሉ ተቃዋሚ አለ።በጥላቻ ላይ በተመሰረተ መልኩ ሳይሆንየምንደግፈውና የምንቃወመው ግን በተጨባጭ ማስረጃ ላይ መሆንይኖርበታል። በአገራችን ያለ ባላገር ሲናገር «አህያ የምትወድደው ን አጋሰስ አይጠላም» የሚል አነጋገር አለ። ለመሆኑየምንኖርባት ኢትዮጵያ ትናንትም ለመጣው መንገደኛ ዛሬም ለመጣው ሁለተኛ መንገደኛ የተለየ የሕሊና እየት የምትፈጥረው ለምንድን ነው? በእርግጥ ፈራጁ ሕሊና አይደለም ልብ ነው። በአገራቸው ቱሪስት ሆነው ከውጭ አገራት(አኅጉራት)ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ብዙ ሰዎች (ዲያስፖራዎች) እንደኔ ኢትዮጵያን በትክክል ማግኘታችሁን እገምታለሁ። «ኢትዮጵያ ወይም አገራችንን እንዴት አገኘኃት ?»ብለን ስንጠይቃቸው «ኦ ! ኢትዮጵያ ብዙ ለውጥ አሳይታለች ።በጣም ብዙ! ለውጥ አለ።»ይባላል።የተሰሩ በርካታ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴሎች ስፋትና ውበት፣ በቦሌ፣ሜክሲኮ፣ፉሪ፣ጀሞ፣ሲኤምሲ፣ዓለም ባንክ መንገድ የተገጠገጡትን ሕንፃዎች ማማርና ግዝፈት፤ የቀለበት መንገዱን ሥራ መገባደድ፣የጋዜጣና የመጽሔቶች እንደ ልብ በሙሉ ነጻነት መጻፍ ይነግሩአችኋል። የአገሪቱን እድገትና ውድቀት ፣መዋብና መጥፋት የምንመለከትበት ዓይንና መነጽር እየተለያዩ

ኢትዮጵያ ውስጥ በእርግጥ ለውጥ አለ?

➡️ኢትዮጵያ ውስጥ በእርግጥ ለውጥ አለ? ከወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ (ደራሲ፣ጋዜጠኛና ማህበራዊ ሀያሲ)  በስልጣን ላይ ያለው የብልፅ ግና ፓርቲ የፓርቲው ሊቀመ ንበር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትግራይ ክልል የተወሰደውን የሕግ ማስከበር ርምጃ አስመልክተው ለፓርላማ ምላሽ ከሰጡ ሦስት ወራትን አስቆጥረዋል።  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል የተወሰደውን የሕግ ማስከበር ርምጃ አስመል ክተው ለፓርላማ ምላሽ ከሰጡ በኋላ ጁንታው ጠፍቷል ቢባልም ቀንደኞቹ  የወያኔ መሪዎች አሁንም አለመያዛቸው በሕዝቡ ዘንድ አግርሞትን ፈጥሯል።  መሪዎቹ ያሉት ዋሻ ውስጥ ናቸው ቢባልም ዋሻውን ደምስሶ ግለሰቦችን መማረክም ሆነም ማጥፋት አልተቻለም።   እንዲያውም የህወሓት አመራር አባል የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይ ሚዲያ ሀውስ በስልክ ገብተው ባለፈው ሳምንት ላይ «እኔ አደባባይ ላይ ወጥቼ ኢትዮጵያ እናቴ የሚለው ቋንቋ መናገር የምችልበት ሰዓት አይደለም! ጦርነቱ አልቋል የሚባለው ምኞት ነው!» በማለት መግለጻ ቸው ተነግሯል። ይህንን ተንተርሶ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች እየተለ ቀቁ ያሉ ነገሮችን ከማስፈ ራራት ይልቅ ወሬውን እንዲጠራ አልተደረገም።   በእርግጥ መሪዎቹ ዋሻ ውስጥ ከሆኑ የትግራይ ሕዝብ በረሀብ እየተቆላ ባለበት በአሁኑ ወቅት ከየአቅጣጫው የእርዳታ እጅ ሲዘረጋላቸው።እነዚህ ዋሻ ውስጥ ያሉ የጁንታው መሪዎች ዋሻ ውስጥ ይዘውት የገቡት የእህል ዘር የአመት ቀለባቸውን ይሆን? ዋሻውስ መግቢያውና መውጫው አይታወቅም? ዋሻው የተሰራው በኮንክሪት ስለሆነ ነው ከላይ አየር ኃይላችን ቢደበድበው የማይፈርሰው? የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎች እንዲነሱ ያደርጋል።   ከዚህ አንጻር በሕዝቡ ዘንድ ያ

ለኢትዮጵያችን ሰላም ለማምጣት ዘብ እንቁም! ❗️

✅ ለኢትዮጵያችን ሰላም ለማምጣት ዘብ እንቁም! ❗️ ከወሰንሰገድ መርሻ(ጮራ ዘአራዳ) (ደራሲ፣ጋዜጠኛና ማህበራዊ ሀያሲ) ብዙዎቻችን ስለራሳችን እንጂ ስለሌሎች አንጨ ነቅም፣እኛ ከበላን ወይንም ከጠጣን.. ሌሎች ወገኖቻችን በሉ ወይም ጠጡ ግድ የለንም ።በቤታችን ውስጥ እኛ ጋር ሰላም ካለ …ሌላው ጋር ሰላም ኖረ አልኖረ ምንም የማንጨነቅ እንኖራለን።በአካባቢያችን ደግሞ እኛ ጋር ሰላም ካለ … ሌላው መንደር ሰላም ባይኖር ደንታ የሌለን በርካቶች ነን።ግን ግን… የጎረቤታችን ሰላም ማጣት እኛንም እንቅልፍ እንደሚያሳጣን ግን መገንዘብ ያስፈልጋል። መሐል አዲስ አበባ ተቀምጠን ቢራ፣ድራፍት፣አዘን ለአንድ ሰዓትና ከዛ በላይ እንደ ተኩስ ሻይ ፉት… ፉት እያልን ፤ አሊያም የጀበና ቡና በአምስት ብር አዘን ፤« የቡና ስባቱ .. »የሚባለውን ወደ ጎን ትተን የቀረበልንን የሲኒ ቡናችንን ከንፈራችን ጋር ለበርካታ ደቂቃዎች እያስጠጋን … እየመለስን ...ወይም ቡናውን ሳንጣጥመው ጠጥተን አሊያም ተራና አሉባልታ ወሪያችንን እየሰለቀጥን የሲኒው ቡና ቀዝቅዞ ዳግመኛ ለማሞቅ የምንሻም ጊዜ አሳላፊ ሰሪና አሰሪ ፤ሻጪና አገናኝ ነን ባዮች እነቱሪናፋ የሆኑ ወገኖችም እንደዛው በርከት ያሉ ናቸው ። ሃገራችን በጦርነት እየታመሰች ነው።የእሷ መታመስ ለአንዳንዶቻችን ምንም አይደለም፦የጥይት እሩምታና የከባድ መሣሪያ ድምድምታ ባንሰማም ፤ በየማህበራዊ ሚዲያው ተለጠፎና በየመገናኛ ብዙሆን ጭምር በጣም አሳዛኝ ነገሮችን እያየን እንዳላየን፤እየሰማን እንዳልሰማን መስለን የምንኖርም በዛው ልክ አንታጣ ም።ለመሆኑ ለኢትዮጵያችን ሰላም ለማምጣት የምንጥር በየቤቱ፣በየሰፈሩ፣በየጓዳ ጎድጓዳው .… የምንገኝ ስንቶቻችን

ለሰው ሞት አነሰው ! » አለች ቀበሮ

➡ «ለሰው ሞት አነሰው ! » አለች ቀበሮ ከወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ (ጮራ ዘአራዳ ) (ደራሲ፣ጋዜጠኛና ማህበራዊ ሀያሲ) ሰውዬው ወንዝ ሊሻገር ይልና የቁም ውኃ ያገኛል።ስለዚህ ለመሻገር እየዋኛ መሄድ አለበት። በመሆኑም እየዋኛ ሲሄድ ትልቅ እባብ ያገኛል። እባብም ሰውየውን« አሻገረኝ !» አለው።ሰውየውም መልካም ነገር ማድረግ ጥሩ ነው ይልና እባቡን እራሱ ላይ ጠምጥሞ ካሻገረው በኋላ «በል አቶ እባብ ወንዙን ተሻግረሀል! ቶሎ ውረድ ...» ይለዋል። እባብም «አልወርድም ...!»ብሎ ያስቸግረዋል።   ሰውየውም በመጀመሪያ ለዳኝነት ይልና የአውሪዎች በሙሉ ንጉሥ ወደ ሆነው  አንበሣ ጋር ሄዶ ከእባብ እንዲገላግለው ደኝነት ይጠይቀዋል። አንበሣም እባብ ተንኮለኛ ብቻ ሳይሆን ቂመኛም መሆኑን ስለሚረዳ። አንበሣ «አደና ላይ ሆኜ ቢነድፈኝስ...?» ይልና ፈርቶ ሰውየውን እንቢ ብሎት ወደ ጦጢት ይልከዋል። እንደተባለው ጦጢት ጋር ሄዶ ዳኝነት ይጠይቃታል። መለኛዋ ጦጣም ፍየልና ቀበሮ እባብን ከገደሉ በኋላ ከነደፋቸው የሚበሉት ቅጠል  እንዳላቸው ስለምታውቅ።ወደ ፍየልና ወደ ቀበሮ እንዲሄድ ትመክረዋለች። እናም ሰውየው ሲሄድ ፍየል የለችም። ይሁንና ቀበሮን ያገኛል። ከዛም ሰውየው ቀበሮን እጅ ከነሳ በኋላ «ዳኝነት አጥቼ እየተጉላላው ነው እባክ ዳኝነት እፈልጋለሁ እርዳኝ !» ይለዋል። ቀብሮም «ደኝነት የሚሰጠው በዳይና ተበዳይ ጎን ለጎን ሆነው ነው እንጂ እንዱ ጭንቅላት ላይ ተጥምጥሞ ሌላው ቆሞ አይደለም።ስለዚህ ሁለታችሁንም እኩል እንድዳኝ እባክ  እባብ መጀመሪያ ከተጠመጠምክበት ከሰውየው  ጭንቅላት ውረድና ዳኝነት እሰጣችዋለው !» አለች ። እባብም ወረደ ።ቀብሮም ለሰውየው በያዘ

«ናርሲዝም» ዎችና ሬሳ ማሺ ዎች!

➡ «ናርሲዝም» ዎችና ሬሳ ማሺ ዎች! ከወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ (ደራሲ፣ጋዜጠኛና ማህበራዊ ሀያሲ) ሰውዬው ወንዝ ሊሻገር ይልና የቁም ውኃ ያገኛል።ስለዚህ ለመሻገር እየዋኛ መሄድ አለበት። በመሆኑም እየዋኛ ሲሄድ ትልቅ እባብ ያገኛል። እባብም ሰውየውን«አሻገረኝ !» አለው።ሰውየውም መልካም ነገር ማድረግ ጥሩ ነው ይልና እባቡን እራሱ ላይ ጠምጥሞ ካሻገረው በኋላ «በል አቶ እባብ ወንዙን ተሻግረሀል! ቶሎ ውረድ ...» ይለዋል። እባብም «አልወርድም ...!»ብሎ ያስቸግረዋል።   ሰውየውም በመጀመሪያ ለዳኝነት ይልና የአውሪዎች በሙሉ ንጉሥ ወደ ሆነው  አንበሣ ጋር ሄዶ ከእባብ እንዲገላግለው ደኝነት ይጠይቀዋል። አንበሣም እባብ ተንኮለኛ ብቻ ሳይሆን ቂመኛም መሆኑን ስለሚረዳ። አንበሣ «አደና ላይ ሆኜ ቢነድፈኝስ...?» ይልና ፈርቶ ሰውየውን እንቢ ብሎት ወደ ጦጢት ይልከዋል። እንደተባለው ጦጢት ጋር ሄዶ ዳኝነት ይጠይቃታል። መለኛዋ ጦጣም ፍየልና ቀበሮ እባብን ከገደሉ በኋላ ከነደፋቸው የሚበሉት ቅጠል  እንዳላቸው ስለምታውቅ።ወደ ፍየልና ወደ ቀበሮ እንዲሄድ ትመክረዋለች። እናም ሰውየው ሲሄድ ፍየል የለችም። ይሁንና ቀበሮን ያገኛል። ከዛም ሰውየው ቀበሮን እጅ ከነሳ በኋላ «ዳኝነት አጥቼ እየተጉላላው ነው እባክ ዳኝነት እፈልጋለሁ እርዳኝ !» ይለዋል። ቀብሮም «ደኝነት የሚሰጠው በዳይና ተበዳይ ጎን ለጎን ሆነው ነው እንጂ እንዱ ጭንቅላት ላይ ተጥምጥሞ ሌላው ቆሞ አይደለም።ስለዚህ ሁለታችሁንም እኩል እንድዳኝ እባክ  እባብ መጀመሪያ ከተጠመጠምክበት ከሰውየው  ጭንቅላት ውረድና ዳኝነት እሰጣችዋለው !» አለች ። እባብም ወረደ ።ቀብሮም ለሰውየው በያዘው ዱላ እባብን ቀጥቅጦ እንዲገለው ምልክት ሰጠችውና ሰውየውም በያዘ

ማነው መሪያችን ?

ማነው መሪያችን ? ከወሰንሰገድ መርሻ (ጮራ ዘአራዳ ) ትውልድ ትውልድን እየተካ አሁን ያለንበት ደረጃ ደርሰናል።  የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዘመነ መሣፍንት ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ይበጀኛል ብሎ የመረጠው መሪ በጭራሽ የለም።አገሪቱን ሲመሩ የነበሩት አብዛኛው ነገስታቶችም ሆነ ፖለቲከኞች ስልጣን ላይ የወጡት በጡቻ ነው።  ከዚህ በፊት የነበሩ ነገሥታቶች አገሪቱን እንዲመሩ ከፈጣሪ የተሰጣቸው ጸጋ አድርገው ነበር የሚመለከቱት። ሌላው ቀርቶ ከ14 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ክብረ -ነገሥት እስከ ቀደማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት ድረስ ዋጋ የሚሰጠው መጽሐፍን ተንተርሰው  ለሰባት መቶ ዓመታት ያህል በኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ  ሕገ-መንግሥት ሆኖ እንዳገለገለና ከ1270 እስከ 1966 ዓ.ም በኢትዮጵያ የነገሡት ነገሥታቶቻችን በሙሉ ሥልጣናቸው ይወሰን የነበረው በዚሁ «ክብረ -ነገሥት» በሚደነግገው ሕግ መሰረት ነበር።  ፍካሬ ኢየሱስ ተቀነባብሮ ከመጣበት ከአሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ታሪክ የፈለቁ ባሕታውያንና መናንያን ድርሳኑን ለመስበኪያና ምዕመናን ለመገሰጽ ተጠቅመዉ በታል። ባሕታውያን በሰለሞናዊው ሥርወ -መንግሥት ስም የነገሱ ክርስቲያን  ነገሥታት ከፍተኛ ተቀባይነት ስለነበራቸው ስለሚመጣው ዘመን ሁኔታ በቤተ መንግሥት የነበሩ ነገሥታት ይጠይቋቸው  ነበር።ይህ ብቻ አይደለም ኢትዮጵያን የመሩ ነገሥታቶች የሚገጥማቸው የአስተዳደር ችግር እንዲሁም  የመጻኤ ሕይወታቸው ሁኔታ የተሳካ እንዲሆንላቸው ባሕታውያንን በሱባኤና በጸሎታቸው ፈጣሪ እግዚአብሔር እንዲጠየቁላቸው ይማጽኗቸው ነበር። ባህታውያንና መናንያን ግን የፍካሬ ኢየሱስ ጭብጦችን ከማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 24 ጋር በመጥቀስ ያስፈራሩና ትንቢቱም ደርሷል እያሉ ይገልጹ ነበር።ይህ አይነቱ ሁኔታ ከኢትዮጵ

ለኢትዮጵያችን ሰላምና ነፃነት ወሳኞች ናቸው

✅ ለኢትዮጵያችን ሰላምና ነፃነት ወሳኞች ናቸው ! ከወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ (ደራሲ፣ጋዜጠኛና ማህበራዊ ሀያሲ) «ሰው ማለት ደፋር የማያወላውል ፣ያለድርድርና ማካካስ በእራሱ መርህ ብቻ የሚተዳደር ወይም የሚኖር፣የማንም ስሜት መማረክና ድጋፍ ወይም አለኝታ የማይጠበቅ ፣የሚገኘው መልካም ውጤት ወይም የሚጎናፀፈው ድል የግሉ ጥረት ውጤት የሆነ ፣ውድቀቱ ከእሱ ቁጥጥር ወይም አቅም በላይ በሆነ አደጋ ቢከሰት እንኳን ጥፋቱን ወይም ውድቀቱን ያለ ልመና እና ይቅርታ ሣይደነግጥ በረጋ መንፈስ በድፈረት የሚቀበል ነው።»ደራሲ ዊልበር ስሚዝ    «Men of Men» በሚለው መጽሐፉ ላይ ነበር ስለ ሰው ልጅ ያለውን አመለካከት የገለጸበትን ሁኔታ ነበር ለመግቢያነት የተጠቀምኩበት። ማንኛውም ሰው መልካም ውጤት  የሚጎናፀፈው በግሉ ጥረቱ ለሽንፈት ሳይዳረግ ካስበበት ቦታ ሲደርስ ብቻ ነው።የሰው ልጅ በሕይወቱ ውስጥ በርካታ መሰናክሎች ያጋጥሙታል። እነዚህን መሰናክሎች ለማለፍ ደግሞ ትዕግስትና ብልሀት ያስፈልገዋል።   የሰው ልጅ ካለፈው ውድቀቱ የሚማር ነው።ቁጥጥር ወይም ከአቅሙ በላይ ወይንም ሊቆጣጥረው የማይችላቸው ነገሮች ወይንም አደጋዎች በሚያጋጥሙበት ጊዜ እንኳን ጥፋቱን ወይም ውድቀቱን ቶሎ ብሎ የመቀበልና ከተጋረጠበት አደጋ ለመውጣት በአብዛኛው ወደ አምላኩ መማጸንን ይመርጣል።በአብዛኛው የሰው ልጅ ሽንፈትን አሜን ብሎ መቀበል የማይፈልግ ፤ትልቅ አላማና ግብ ይዞ የሚጓዝ፤ ሕይወቱን አሁን ካለበት ሁኔታ ማሻሻልና ማደግ የሚፈልግ ፤መወደቅ እንዳለ ሁሉ መነሳትን የሚሻ ፤ሀብታም ለመሆን እንደምንሻ ሁሉ መደየትም እንዳለ መገንዘብ ያስፈልጋል፤መኖርን እንደምንወደ ሁሉ አንድ ቀን  እንደ ምንሞትም  ማወቅ ወዘተ.በቅድሚያ ማወቅና  መገንዘብ አለበን።ዓለም የሁለት ተቃራኒ መድረኮች ና

የዘር ፖለቲክስ(race politics)

የዘር ፖለቲክስ(race politics) (ከወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ) (ደራሲ፣ጋዜጠኛና ማህበራዊ ሃያሲ) የዘር ፖለቲክስ(race politics) የሰው ልጅ ሕይወትና ንብረት አውዳሚ መሆኑን በዓለም ላይ አይተናል ።ሌላው ቀርቶ በሀገራችንም ውስጥ ምን አይነት ጉዳት እንዳደረሰ ተመልክተናል።  ዘረኝነት በዓለም ላይ ከፍተኛ ጉዳት አምጥቷል። በተለይም ጀርመናውያን አይሁዳዊያንን ለማጥፋት በጥቂት መሪዎቻቸው የተነሳ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ለመቀስቀስ በቅቶ በርካታ ሰዎች ለሞትና ለመቁሰል አደጋ ደርሰዋል።ከተሞች እንዳልነበረ ፈራርሰዋል። በርካታ ንብረቶች ወድመዋል፣ ወዘተ. በተለይም  ለስድስት አመታት ያህል በተካሄደው የሁለተኛው የዓለም ጦርነት የሞቱትና የቆሰሉት ተደምረው በሰው ክጅ ህይወት ላይ የደረሰው ጉዳት 54,800,000 አካባቢ ይደርይደርስ ነበር።  የጦርነቱ ሰለባ በወቅቱ የነበሩት በአብዛኛው ፖላንዳውያን ነበሩ። በዚህ ጦርነት 6,028,000 ወይም 22.2 በመቶ የሚሆነው ፖላንዳውያን አልቆ ነበር።   በዚህ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት 25 ሚሊዮን ጉዳተኞች የሆኑት የሶቪዬት ህብረት ዜጎች እንደነበሩ አይዘነጋም ። 7,800,000 የቻይና ዜጎችም በዚሁ ጦርነት ህይወታቸውን እስከማጣት የደረሱበት ወቅት ነበር።  በዚህ በአህጉራችንም በተከሰተው የዘረኝነት ሁኔታ ሩዋንዳን ማንሳት ይቻላል። በሁቱና በቱትሲ የደረሰውን እልቂት ማሰቡ በቂ ነው። በተለይም ዘር-race በሂትለር ዘመን እስራኤላዊያንን ለእርድ አቀረቧል።እንዲያውም ሰውን እንደ ጦጣ እና ዝንጀሮ የሳይንስ መመራመሪያ እስከ ማድረስ ደርሰውም እንደነበር ማስታወሱ በቂ ነው ።    ዛሬ ዓለም ከዚህ ዘረኝነት ባስነሳው ጦርነት ብዙ ነገር ተምረው ወደ አንድ እየመጡ  ባለበት በአሁኑ ወቅት በእኛይቱ