Posts

Showing posts from May, 2019

«ጋዜጠኝነትን ስትሰራ የጋዜጠኝነትን ኮፍያ ታረጋለ፤ አክቲቪስትም ስትሆን እንደዛው፤ ፖለቲከኛ ስትሆን የፖለቲካ ኮፍያ ታደርጋለ ዋናው የምትሰራውን ማወቅ ላይ ነው» ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ

Image
ጋዜጠኝ፣ አክትቪስትና ፖለቲከኛ እስክንድር  ነጋ አንዳንድ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች የአዲስ አበባ ባላደራ ኮሚቴን ማቋቋሙን አስመልክቶ እየተሰነዘረበት ያለውን ትችት እንደማይቀበለው ገለጸ።    እስክንድር በፕሬሱ ላይ ከፍተኛ መስዋትነት ከከፈሉት ጋዜጠኞች በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው። በመሆኑም በአሁኑ ወቅት ከስር ከተፈታ በኋላም «ኢትዮጲስ» ጋዜጣን በማሳተምና በማዘጋጀት ላይ ይገኛል። ጋዜጣው ዘወትር ቅዳሜ በየሳምንቱ ስትወጣ በርካታ ውጣውረዶችን አይታ  ነው ለአንባቢው የምትበቃው። በሌላ በኩል እስክንድር አክቲቪስትም ነው ከዚህ ሌላ የአዲስ አበባ ባላደራ ኮሚቴን በማንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። ለእስክንድር ብዙ ሰዎች አንተ ከምትታወቅበት የጋዜጠኝነት ሙያ ባሻገር ፖለቲካና አክቲቪስት መሆንህን በብርቱ  ይቃወማሉ ለዚህ ያለክ አስተያየት ምንድን ነው አልኩት ? እስክንድርም «ይሄ በጣም ደስ የሚል ጥያቄ ነው ፤ለእኔ ሁሉንም በአግባቡ መምራት ትችላለ  ባይ ነኝ ። ጋዜጠኝነትን ሙያ ስትሰራ የጋዜጠኝነትን ኮፍያ ታረጋለ፤ አክቲቪስት ስትሆን እንደዛው ፤ፖለቲካን ስትሰራ የፖለቲካ ኮፍያ ታደርጋለ ዋናው  ቁምነገር የምትሰራውን ስራ ማወቅ ላይ ነው » ይላል።  «ጋዜጠኝነቱን ስትሰራ ከማንም ፖለቲካ ሳትወግን የራስህንም የፖለቲካ አመለካከት ሳታራምድ ሚዛናዊ ሆነ ትክክለኛውን ነገር መሥራት ነው። አክቲቪስትም ስትሆን እንደዛው ፖለቲከኛም ስትሆን መስራት ያለብህን ነገር መስራት ነው »በማለት ይገልጻል።   እንደ እስክንድር  በርካታ ተዋቂ የእንግሊዝም ሆነ የሌሎች ሀገር ጋዜጠኞች የራሳቸውን ፖለቲካ እያራመዱና እየተንቀሳቀሱ በአንፃሩ ዋንኛውን የጋዜጠኝነት ሙያቸውን እየሰሩ ይገኛሉ በማለት ከገለጸ በኋላ የእሱም ሁኔታ በአሁኑ ወቅት ከዚሁ ያልተለየ መሆኑን  ይጠቁማል 

ዕድሜ ልካችንን «ሰይ ብል ባንከረባብት …» ከጋዜጠኛ ወሰንሰገድ መርሻ

Image
የነፃው ፕሬስ ከታወጀ እነሁ ሁለት አሥርተ አመታትን አስቆጥሯል።በነዚህ አመታት ውስጥ የተለያዩ ውጣ ውረዶችን ፕሬሱ አሳልፏል።    ከመንግስት ጋር የሚደረገው «የሌባና ፖሊስ ጨዋታ ..» እንዳለ ሆኖ ሌላው የፕሬሱ አባላት ማለትም ጋዜጠኛው፣አሳታሚው፣አከፋፋዩ፣አዟሪው ጋር ያለው የእርስ በርስ ሽኩቻ በዋንኛነት ይጠቀሳል።   ያለፉትን አመታቶች ወደ ኋላ ተመልሶ መመልከቱ ጥቅም የለውም አባቶች እንደሚሉት «ላለፈ ክረመት ቤት አይሰራም ..»ስለሚሉ  አንባቢን እንደ ኦለቲከኞች ማድንቆር ስለሚሆንብኝ ባለፉት ሁለት አመታት የታዘብኩትን  ብቻ በብዕሬ አንድ ለማለት ወደድኩ ። በነገራችን ላይ እንደሰዉ በወረቀት ላይ ጫጭሬ ከዛ በላፕቶፕ ላይ ወይንም በኮሚፕተር ላይ አጽፌ ወይንም ጽፌ አይደለም ይህንን ጽሑፍ ጽፌ ብሎጌ ላይ ወይንም የነፃ ድህረ ገጼ ላይ የምለጥፈው  ብቻ በቀላሉ የምሰራው ሁሉ ነገር በሞባይሌ ስለሆነ የተጣመመውን አስተካክላችሁ የጎበጠውን አቅንታችሁ እንደምታነቡልኝ ተስፋ አድርጋለሁ።ድህረ ገፆቼ በነፃ ስለሆነ እንደሌሎች ድህረገጾች ለአንባቢው ቶሎ እንደማይደርስ ስለማውቅ ፊስቡክንና ትዊቴርን ሼር በማድረጉ በኩል ስለምጠቀም ይሄ ደካማ አንባቢ የሌለው ጸሐፊ እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ።   ወደ ዋናው ነጥቤ ልመለስ የኢትዮጵያ ነፃ ፕሬስ ጋዜጠኞች ላለፉት በርካታ አመታት በሁለት ተከፍለው እየተሻኮቱ ነው አመታትን ያስቆጠሩት አንደኛው ለሆዱ ያደረ በወያኔ የሚደገፍ ብዕረኛ ወይንም ጋዜጠኛ ሌላኛው ለህሊናው የኖረና የሚኖር ነበር። አሁንም እንዳለፉት ጊዜያት አይብዛ እንጂ ለህሊናው የሚጽፍ  ብዕረኛ አሊያም የሚሰራ ጋዜጠኛ አናሳ ቢሆንም  የአመራር ፊደል አጣጣሉ፤ የቃላት አገባቡ፤የዐርፍተ ነገር አሰካኩን ወደኋላ ትተን ዝም ብሎ ጫጫሪ የሚለውን ይዘን

ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን የሚያፍነው መንግስት ብቻ ነው? (በመስከረም አበራ

Image
በመስከረም አበራ ሃገራችን ለረዥም ዘመናት በተፈራራቂ አምባገነኖች ክርን ስትደቆስ በመኖሯ ሳቢያ ሃሳብን የመግለፅ ነፃነት እጅጉን ተጎድቶ ኖሯል፡፡ በነዚህ አምባገነን መንግስታት ዘመን መናገር ከተቻለም የሚቻለው እነሱኑ ከነአፋኝ ማንነታቸው ለማወደስ ነው፡፡ በተቀረ እውነቱን ለመናገር ከሆነ ሃሳብን መግለፅ ብዙ ዋጋ ያስከፍላል፡፡አምባገነኖቹ ገዥዎቻችን አፈናን የሚያስኬዱበት መጠን፣ተችዋቻቸውን ለማሳደድ የሚሄዱበት ርቀት ብዙ ሲባልበት የኖረ ስለሆነ ያንን መደጋገም የዚህ ፅሁፍ አላማ አይደለም፡፡የዚህ ፅሁፍ አላማ በሃገራችን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ተግዳሮት የሚመጣው ከመንግስት ብቻ እንዳልሆነ ከየሁት እና ካጋጠመኝ ተነስቼ ማሳየት ነው፡፡ በሃገራችን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ከመንግስት ብቻ የሚመጣ ተግዳሮት እንደሆነ በሰፊው ይታመናል፡፡ይህ የሆነው መንግስት እስርቤት ስላለው የማይፈልገውን ሃሳብ የሚያነሱ ሰዎችን ወደእስር ቤት ሲያጉር ስለሚታይ ነው፡፡ነገር ግን እስርቤት የሌላቸው፣እንደ አምባገነኑ መንግስት የፖለቲካ ስልጣን ያልያዙ አፋኞች በሃገራችን ሞልተዋል፡፡ እነዚህ አፋኞች ምናልባትም ከእነሱ የበለጠ ጉልበት ባለው አምባገነን መንግስት “ሃሳብን ስለመግለፅ መብት ሲታገሉ” ሲታሰሩ ሲፈቱ  የምናያቸው፣መንግስትን በአፋኝነቱ ሲያብለጠለጥሉ የኖሩ  የሚዲያ ሰዎች፣የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሃሳቡን በመግለፁ፣ጋዜጣ በማሳተሙ መንግስት ያሰረው ሁሉ ሃሳብን የመግለፅ መብት የሚያከብር፣ከአፋኙ መንግስት የሚሻል ነው ማለት አይደለም፡፡በኢትዮጵያ ፕሬስ ውስጥ በአምደኝነት በተሳተፍኩባቸው ዘመናት ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት አፋኙ ህወሃት መራሹ መንግስት ብቻ እንዳልሆነ በደምብ ተረድቻለሁ፡፡ስለዚህ በሃገራችን ሃሳብን በነፃነት ስለመግለፅ

ኢትዮጲስ -- ከአረንጓዴ ወደ ቢጫ መብራት ከጋዜጠኛ ወሰንሰገድ መርሻ

Image
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን  ዶክተር አብይ ስልጣኑን ከአቶ ኃይለ ማርያም  ከተረከቡ ጊዜ አንስቶ ከታዩ ለውጦች መካከል ከተዘጉ ድህረ ገጾችና ብሎጎች በተጨማሪ ለበርካታ አመታት ከገቢያ ውጪ የነበረችው የነፃው ፕሬስ  ፈር ቀዳጅ የሆነችው የ«ኢትዮጲስ» ጋዜጣ አዘጋጅና ባለቤት መፈታትና ጋዜጣው የመጀመሩ ሁኔታ ይገኛል  ።   የጋዜጣው ባለቤትና አዘጋጅ  የሆነው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ለበርካታ አመታት በእስር ሲማቅቅ ከቆየ በኋላ ከእስር ተፈቶ ጋዜጣውን ከጀመረ 36  እትሞችን ለተደራሲዮና አቅርቧል ።ይህም በወራት ሲሰላ  ጋዜጣው 9 ወራትን አስቆጥሯል።    «ኢትዮጲስ» የነፃው ፕሬስ ፈር ቀዳጅ በመሆኗም ትታወቃለች።ዛሬ ጋዜጣዋ እዚ ደረጃ የደረሰችው እስክንድርን ጨምሮ በርካታ ጋዜጠኞች መስዋትነት ከፍለው ነው።በተለይም ነፍሳቸውን ይማረውና ዛሬ በሕይወት የሌሉት ወዳጆቼ ጋዜጠኛ ተፈራ አስማረና ጋዜጠኛ ወርቁ አለማየሁ ዋናና ምክትል አዘጋጅ ሆነው፤ጋዜጠኛ ጌታመሳይ ገመስቀል(ኩሹ) ደግሞ ጋዜጣውን በማከፋፈል (በርካታ ተዋቂ መጽሔትና ጋዜጣ አከፋፋዮችን ፍቃዱን((ባሪያውን) ፤መኮንንን ወዘተ.ያፈራ ጭምር ነው) ከእስክንድር ጋር በመሆን ትልቅ አስተዋጾ በወቅቱ አድርገዋል።   እነዚህ የሞቱ የ«ኢትዮጲስ» ባለውለተኞች እንደ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጥሩ ወዳጆቼ ብቻ ሳይሆን ጥሩ ቀረቤታ እስከ ቤተሰብ  ጭምር ድረስ ነበረን ። አራት ኪሎ ከመፈራረሱ በፊት።ከተፈራ አስማረና ከጌታመሳይ (ኩሹ) ጋር አንድ አካባቢና አንድ ቀበሌ ውስጥ መኖር ብቻ አይደለም የሰፊ ሰፈርና የቀበሌ 07 ዕድር ውስጥ በቤተሰብ ደረጃ በሐዘንም በደስታም ተካፋይ አብረን ነበር ከተፈራ አስማረ ወንድሞች ከሞቱት ከአምባውና ከቴዲ ከሌሎቹ እህቶቹ ጋር ቀረቤታ ነበረኝ ከዚህ ሌላ ከአባቱ   ከአቶ አስማረ

Several times Jailed !.. My Best Jourenalist ..Eskender Nega

Image
Before US Educated ,Several times Jailed Now Weekly News Paper Ethiopis Editor & Chief Jourenalist Eskinder Nega & Jourenalist Wosenseged Mersha Eskinder Nega, a journalist and blogger based in Addis Ababa, was sentenced on July 13, 2012, to 18 years in prison for violating anti-terrorism laws after he criticized the government for arresting journalists and anti-government activists. He was jailed for almost seven years at Kaliti Prison in Addis Ababa, where political prisoners are housed with criminals and family visits are extremely limited, before being released on February 14, 2018, as part of a larger amnesty of political prisoners. On the evening of March 25th, 2018, the Ethiopian Security Forces have re-arrested Eskinder and other journalists and politicians at a social event outside the capital, Addis Ababa. Eskinder was accused of displaying a prohibited national flag and gathering in violation of an official state of emergency but was later r

After years of repression, Ethiopia’s media is free — and fanning the flames of ethnic tension

Image
A man walks by a newsstand in Addis Ababa, the capital. (Paul Schemm/The Washington Post) By  Paul Schemm   April 21, 2019 at 6:00 AM EDT ADDIS ABABA, Ethi­o­pia — From a collection of modest offices in a half-empty high rise, one of Ethiopia’s most prominent journalists publishes his weekly paper with a staff of just four. The country has imprisoned U.S.-educated Eskinder Nega multiple times, most recently for six years. But under Prime Minister Abiy Ahmed’s government, he and some dozen other jailed journalists have been released and are free to write. His new weekly Ethiopis takes a strident tone, especially against the city administration and activists from Ethiopia’s Oromo ethnic group, newly empowered by their fellow Oromo, Abiy. He sees his paper and his activism as part of his long struggle for democracy.   Others see it as a danger to Ethiopia’s delicate political state and as part of a wave of news outlets that are taking sides and worseni

የኢትዮጵያ ነፃ ፕሬስን ከአድርባዮችና ከሆዳሞች ለማጽዳት ለሙያው መስዋት የከፈሉ ሁሉ በየፊናቸው ሊታገሉ ይገባል

Image
የኢትዮጵያ ነፃ ፕሬስን ከመንግስት ፕሬስ ጋር ለመቀላቀል የግል ፕሬሱ ፕሬዝዳንት ነኝ በሚሉት  በመቶ አልቃ ወንድወሰን መኮንንና (አሁን አቶ) በመንግስት ጋዜጠኞች ፕሬዝዳንት  በአቶ መሰረት አታላይ  የመንግስት ጋዜጠኞች ማህበር የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት የመሥረታ ምክንያት በማድረግ ሚያዚያ 29ቀን በተከበረበት ወቅት መገለጹን በግንቦት ወር በወጣው በ«ግዮን» መጽሔት ላይ አንብቤ ነበር።  የነነፃው ፕሬስ ፕሬዝዳንት በአሁኑ ወቅት መሆኑን  የሚያምነው የገዥው ፓርቲ  ከአቶ ክፍሌ ሙላት ይልቅ የቀድሞ መቶ አለቃ የአሁኑ አቶ ወንድወሰን መኮንንን ነው ። በመሆኑም በግል አቶ ወንደወሰንን ይህንኑ በመንተራስ አነጋግሬው ነበር ። በእርግጥ አቶ ወንድወሰንን ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ፕሬስ ውስጥ ከፍተኛ መስዋትነት የከፈለውን እስክንድ ነጋን(የኢትዮፒስ ጋዜጣና የኢትዮጵያ የነፃው ፕሬስ የሥራ አስፈፃሚ አባል የነበረውን) እንዲሁም በስደት ከኢትዮጵያ ውጭ የሚገኙትንና ወደ ኢቱዮጵያ መጥተው እንደኔ ባሉበት ሀገር ኢምባሲ ደንነቶች ሳይታፈኑ ተመልሰው ከመሄዳቸው በፊት ያነጋገርኳቸው በተለይም ለፕሬሱ መስዋትነት ከከፈሉት መካከል በአሜሪካ የሚገኙ እንደ ቢንያም ታደሰ(ሀገሬ ጋዜጣና የቀድሞ የነፃው ፕሬስ ሥራ አስፈፃሚ አባል) እና ሌሎችንም ውጭ ያሉና ኢትዮጵያ ውስጥ በግል ጋዜጣ ላይ ከፍተኛ አስተዋጾ ያደረጉ ጋዜጠኞችን በማነገገር በስደት ያለውና በኢትዮጵያ ያሉ በሁለት ቢለዋ የማይበሉ ጋዜጠኞችን ነበር።  በመሆኑም ኢትዮጵያ ያሉት በግንባር እንዲገኙ ሲደረግ  ሌሎቹ በስደት የሚገኙት ደግሞ በስካይቢ አማካይነት በስብሰባው ላይ ተካፍለው በሰላማዊ መንገድ በሚከናወነው በዚሁ ስብሰባ ላይ ወይ ባለፉት ላይ መጨመር አልያም አዲስ  ምርጫ እንዲከናወን ጋዜጠኞቹን አነጋግሬ ነበር ። በ

«ሕዝቦች የተመረጡ መረጃዎችን ይፈልጋኩ .ፕሬሶች ለዚህ ደግሞ አማራጮች ናቸው» ጀምስ ዲ ዎልፈን ከዩኔስኮ

የኢትዮጵያ አጠቃላይ የመገናኛ ብዙሐን ሕግ በ1992 እ.ኤ.አ የወጣ ሲሆን የብሮድካስቲንግ ሕግ ደግሞ በ1999 እ.ኤ.አ ነው የወጣው ። እራሱን ችሎ የሚዲያ ፖሊሲ መወጣት የጀመረው እ.ኤ.አ ከ2007 ዓመተ ምህረት ጀምሮ ነው። በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ውስጥ የተለያዩ የቴሌቪዥን ፣የሬዲዮና የኅትመት ውጤቶች በመሥራጨት ላይ ይገኛሉ። በሀገሪቱ ውስጥ ያሉትን እነዚህን ሚዲያዎቹ የማንነታቸውን ጥያቄ ወደ ጎን ትተን ። በሚዲያ ዙሪያ ያሉ መረጃ ስለማግኘትና ስለመስጠት ከሕግ አኳያ ያለውን ሁኔታና ሌሎች ተዛማጅ ነጥቦችን ለማንሳት ፀሐፊው ይሞክራል። የመንግስትም ሆነ የግል ሚዲያዎች(ፖለቲከኞች ታብሎይድ ጋዜጦች ነው የሚሏቸው) በአጠቃላይ ሚዲያዎች መንግስትና ሕዝብን የሚያገናኝ ድልድይ ብቻ ሳይሆን መንግስት ያሉበትን ግድፈቶች እንዲያርም መስታወት ሆኖ የሚያገለግሉ፤ በተለይም በሕዝብ ላይ የሚታዩ ቅሬታዎችን በመጠቆምና በማንሳት ይፋ አድርገው በትረ ስልጣኑን ለያዘው (ለሚመራው ለሀገሪቱ ) መንግስት መስታወት ሆኖ የሚያገለግል ነው። በአንድ ወቅት ዩኔስኮ(UNESCO በ2008 እ.ኤ.አ ) በገፅ 111 ላይ ስለ ነፃው ፕሬስ ያነበብኩት ከላይ ላነሳሁት ነጥብ መልስ የሚሰጥ ይመስለኛል። ስለ ነፃው ፕሬስ በዚሁ ገፅ ላይ ያለው ፍሬ ነገር እንዲህ የሚል ነበር « ነፃ ፕሬሶች የሰው ልጅ እድገትን የሚያንፀባርቁ ከመሆኑም ባሻገር በመንግስትና በሕዝብ መካከል የሚያገለግል ፤ሕዝቡ ያሉበትን ችግሮች የሚያንፀባርቅ ነው » ይለዋል ። ከዚህም ሌላ « መንግስት በተለያዩ ጊዜ የሚወስዳቸውን እርምጃዎች አስፈላጊ ወይንም የተመረጡ ወሬዎችን ብቻ ሳይሆን ከመንግስት ጋር ተቃራኒ የሆኑ ነገሮችን በሕዝቡ ላይ የተፈጠሩ ችግሮችና የተለያዩ ብሶቶችን ይፈ የሚያደርጉ ናቸው » ይላ

የፕሬስ ማነቆ ኢትዮጵያ ውስጥ አሁንም አልቆመም ፤ የተዘጉ ፕሬሶች አሁንም ፍቃድ ማግኘት አልቻሉም

Image
ክቡርብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ  ስልጣኑን ከተረከበ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ  በተለይም በፕሬሱ ላይ የታዩ ለውጦች ቢኖሩም በአንፃሩ ከዚህ በፊት ይወጡ ከነበሩ አንዳንድ ጋዜጦች እስካሁን ድረስ ፍቃዳቸውን ማሳደስ አለመቻላቸው ታውቋል።   ይህ የሚያሳየው የፕሬስ ማነቆ ኢትዮጵያ ውስጥ አሁንም  ያለ መሆኑን ነው ። በተለይም የተዘጉ ፕሬሶች አሁንም ድረስ ፍቃድ ማግኘት አለመቻላቸውን ለማወቅ ተችሏል።  እስካሁን ፍቃድ ዳግመኛ ጠይቀው ከተከለከሉት መካከል በፕሬሱና በሚዲያ  ላይ ለረጅም አመታት የሰራውና «መሰናዘሪያ» የተሰኘው ጋዜጣ ሲሰራ ቆይቶ ፍቃድ አሁንም የተከለከለው  ወሰንሰገድ መሸሻ ይገኝበታል። የጋዜጣው አዘጋጅና ባለቤት  የሆነው ጋዜጠኛ ወሰንሰገድ መሸሻ እንደሚገልጸው «በቀጥታ ባያግዱኝም ማተሚያ ቤቶቹ እንዳላሳትም አድርገውኝ ከመስመር ወጥቻለው» ይላል። «ብዙ ዎቹ እኔን የማያውቁ ሰዎች በገንዘብ እጥረት ወይንም በማነጅመንት ወይንም በአመራር ብቃት ማነስ አሊያም አድረጃጀታችን የተበላሸ ሆኖ ጋዜጣችን የወደቅን ሊመስላቸው ይችላል ። እኔ  ይህንን ለማንም ተናግሬ አላውቅም ነገር ግን የዘጋብን መንግስት ነው የሚል ጥርጣሬ አለኝ፤ምክንያቱም ማተሚያ ቤቱ ያለምክንያት አለስቆመንም  ይህንንም የማቆም ስልጣንም በእርግጥ ማተሚያ ቤቱ አልነበረውም ። በወቅቱ እስከ 15 ቀን ሁሉንም ጋዜጦች አስቆሙ ከ15 ቀን በኋላ ግን የስፖርቶቹን ጋዜጣ መለሱ እኔንም የስፖርቱን ጋዜጣ  ስራ ተብያለው በእርግጥ ፍላጎቱም ዝንባሌውም ችሎታውም ስለሌለኝ እዛ ላይ አልሰራም ብዬ ነበር የሳይንስ ጋዜጣ ማሳተም ከጀመርኩ በኋላ ግን ጋዜጣውን ስንሳያቸው አሁን መጥተ አሳትም ነው ማተሚያ ቤቶቹ ያሉኝ፤ ከዚህ አንፃር ፖለቲካ እንዳላሳትም በወቅቱ ማተሚያ ቤቶቹ መከልከላቸውን

ማንን የፕሬስ እና የሚዲያ አገልግሎትን እንመን? ኢሳት የግንቦት 7 ከሆነ ፋና የኢህ አዲግ ቢሆን ምን ስህተት አለው?የግል ጋዜጦችስ የተቀዋሚና የመንግስት.…? ከጋዜጠኛ ወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ

Image
ሰሞኑን ስድስት ፓርቲዎች እና አንድ ስብስብ ተጨፍልቀው የኢትዮጵያ  ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ  ፓርቲ በመባል እራሱን የሰየመውን  የዜግነት ፖለቲካን ፓርቲን ድርጅትን  የሚመሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ቀድሞ ይመሩት የነበረው ፓርቲያቸው የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ  የኢትዮጵያ  ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) እና  ነፃነት አሳታሚዎች የተባሉትን ያቋቋሙት ንቅናቄው መሆኑን ሚያዚያ 29 ቀን በአዲስ አበባ ከመላው ኢትዮጵያና ከሌሎች የአለማችን ክፍሎች የተሰበሰቡ አባላቱ በተገኙበት ጠቅላላ ጉባሄ  ባደረገበት ወቅት ውሳኔዎችን ባሳልውፈበት ወቅት መግለጹን «ግዮን» መጽሔት ቅፅ 1 ቁጥር 55 ግንቦት 2011ዓ.ም በገፅ 2 ቁጥር 5 ጀምሮ  ንቅናቄው ያሳለፈውን  ውሳኔ አውጥቷል።  እኔ እንደ ጋዜጠኝነቴ ያፈርኩበት ነገር ቢኖር ይኽው ነበር «ጋዜጠኛ ከማንም ፖለቲካ ያልወገነ መሆን አለበት » የሚለውን የተፃረረ ከመሆኑም ባሻገር በወቅቱ የነበረው የኢህአዲግ  መንግስት ስለ ኢሳት ይል የነበርው ነገር እውነታነት ያለው  መሆኑን ለመረዳት ችያለው።  ንቅናቄው  ኢሳትን ያቋቋመው  «የመረጃ አፈናን ለመበጣጠስና በኢትዮጵያ ውስጥ ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል ለማገዝ የግንቦት 7ንቅናቄ ማቋቋሙን ለመጀመሪያ ጊዜ በጉባኤና በአደባባይ » ማመኑን መጽሔቱ ገልጿል።   የመረጃና  የቴክኒክ ድጋፍ ሲያገኝ የነበረው ከሕዝብ ስለሆነ የሃገሪቱ የሚዲያ ህግ በሚፈቅደው አዲስ አስራር መሰረት ተቋሙ አትራፊ ያልሆነ ማህበራዊ ድርጅት ሆኖ እንዲመዘገብ  መታሰቡ ተገልጾ ይህን ተቋም አዲሱ ፓርቲ በባለቤትነትና በበላይነት የሚያስፈጽም አካል ክፍተት እንዳይኖረው በማሰብና  ይኽው አዲሱ ፓርቲ በማያውቀው ጉዳይ ኃላፊነት ውስጥ ገብቶ ችግር ውስጥ እንዳይወድቅ በማሰብ ኢሳትን ከምስረታው ጀምሮ

"of course there is no free press journalist in this time detained person, ( Prisoner ) there is no close blogs,website iIn This Time but There is no Private media in Ethiopia" former Private Journalist Wosenseged Mersha Demissie IFJ & CPJ Corespondent from Ethiopia

Image
The World the 26 free press meeting continue the Africa Nation Office in Ethiopia it also Ethiopia one month ago Reporters Without Border free press Ranked 110th out of 180 countries territories in the 2019 RSF World press Freedom index that Ranking changes like before many things there is no free press journalist detained person, ( Prisoner )there is no Close blogs,website by governmental official . In This Time . but Still The Ethiopia Private media being owned by a private individual or organization rather than by state or public body . i am researched free press news paper, Free Radio & TV Broadcaster a private media the last one & half year . has been owned or sponsored by governmental organization or some other vested interests. Except Eskender Nega News Paper " ETOPIES" The Ethiopia national media police since 2007. The Broadcasting law (1999) and the general media law (1992). The Ethiopia Government EBA Report said 2017 /2018 there

ሰውን በማፈን ኢትዮጵያ ውስጥ የፕሬስ ነጻነት አለ ብሎ መደስኮር የትም አያደርስም ከጋዜጠኛ ወሰንሰገድ መርሻ ደምሴ

Image
ኢትዮጵያ ላለፉት  በርካታ አመታት የፕሬስ አፈናን በማፈንና በማሰር ከኤርትራ በመቀጠል እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የሁለተኛ ስፍራን በመያዝ ግንባር ቀደም ሀገር ነበረች።  የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ስልጣን ከተረከቡ በኋል የተሳሩ ጋዜጠኞች የተፈቱ ከመሆኑም ባሻገር የተዘጉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ድህረ ገጾች ሲከፈቱ በውጭ የሚገኙ የሚታፈኑ በአማርኛ የሚተላለፉ  የሬዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች  የመታፈናቸው ሁኔታ ቀርቶ ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሮ ጭምር ከፍተው እንዲንቀሳቅሱ ተደርጓል ይህ ብቻ አይደለም የተለያዩ  በውጭ የሚገኙ የፖለቲካ አራማጆች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲንቀሳቀሱ ተደርጓል ይህ ኢህአዲግ እንደ አንድ ትልቅ በጎ እርምጃ አድርገን የወሰደው ነገር  እንደሆነ እናምናለን።በዚህም የተነሳ በዓለም አቀፍ የሰበአዊ ድርጅቶችና በጋዜጠኞች ተሟጓቾች ዘንድ ጥሩ ተቀባይነት እንድታገኝ አስችሏታል።  በሌላ በኩል  በሀገራችን  እያየን ያለው  ሁኔታ ግን ለውጥ ሳይሆን ቁማር ጨዋታ መሆኑን በበኩሌ ተገንዝቤአለው ይህ ደግሞ  በኢህአዲግ  ብቻ ሳይሆን በተቀዋሚ  ፖለቲከኞች ጭምር መሆኑ በጣም ያሳዝናል ። በተለይም  ኢህአዲግም ሆነ ላለፉት በርካታ አመታት በውጭና በኢትዮጵያ ተቀዋሚ ሆነው ፖለቲካቸውን ሲያራምዱ የነበሩ ወገኖች ኢትዮጵያ ውስጥ በአሁኑ ጊዜ ሀገራችን ውስጥ እያሳዩት ያለው ሁኔታ በተለይም በኢትዮጵያ ውስጥ ላለነው ወገኖች ለውጥ ሳይሆን ከአራድነትና ከአፍ ጅምናስቲክ ያልዘለለ መሆኑን አብዛኛዎቻችን  ያራዳ ልጆች  የምናውቀው እውነታ  ከመሆኑም ባሻገር ለውጥን ከእግዚአብሔር በስተቀር ማንም እንደማያመጣ ተገንዝበን  በአሁኑ ወቅት የጣለውን ተስፋ በፖለቲካኞች ላይ ቆርጦ አርፎ ተመልካች ሆኖ ቁጭ ብሏል። በፊትም ሆነ አሁን ሁሉም ኢህ አዲግ ካልሆነ ወይንም በፎረምና በ